እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ
#ሰዎች በክርስትና ሕይወት እየቀነሱ ወይም ወደኃላ እየተመለሱ ወይም ደግሞ እየወደቁ እንዳሉ የሚያሳዩ አራት ዋና ዋና ምልክቶች፦
❶ የእግዚአብሔርን ቃል ለማንበብ፥ ለማጥናትና ለመጸለይ ያለው ፍላጎት ከቀን ወደቀን በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ ይመጣል።
❷ ከአማኞች ወይም ከቅዱሳን ጋር መንፈሳዊ ሕብረት የማድረግ፣ አንድ ላይ የመሆን፣ እግዚአብሔርን በጋራ የማምለክ ፍላጎት ከቀን ወደቀን እየወረደ ይመጣል።
❸ በመንፈሳዊ ሕይወት ጠንክሮ ወደፊት የመቀጠል፣ የማድግ ወይም ደግሞ የመጨመር ፍላጎት ቀስ በቀስ እየጠፋ ይመጣል።
❹ ለጥፋቱና ለድክመቱ ዘወትር ምክንያት ይደረድራል ካልሆነ ደግሞ ስለሌሎችን ተጠያቂ ያደርጋል።
Comments
Post a Comment