Posts

Showing posts from May, 2020

መንፈሳዊ እርጅና

Image
#መንፈሳዊ_እርጅና ◆◆◆◆◆◆◆ 📌መንፈሳዊ እርጅና፦በመንፈሳዊ ሕይወት ላይ የሚከሰት እርጅና ዓይነት ስሆን የክርስቲያኖችን መንፈሳዊ ሕይወትን በኃይልና ሁኔታ የሚያጠቃ፣ አልፎም መንፈሳዊ ሕይወትን እስከመግደል የሚደርስ አደገኛ ነገር ነው። 📌መንፈሳዊ እርጅና፦የክርስቲያን መንፈሳዊ ሁለንተናን የሚቆጣጠር፣ መንፈሳዊ አቅምን የሚያሳጣ ሰውን ተራ ክርስቲያን የሚያደርግ አደገኛ የሰይጣን #System ነው። #መንፈሳዊ_እርጅናና_ተፈጥሮአዊ_እርጅና ◆◆◆◆◆◆◆◆◆◆◆◆◆  📌መንፈሳዊ እርጅናን ከተፈጥሮአዊ እርጅና ጋር  የሚያመሳስላቸውም የሚያለያያቸውም ብዙ ነገሮች እሉት። ለምሳሌ  📌ሁለቱም እርጅናዎች ከጤና ችግር ጋር ተያይዞ ይመጣሉ።  ♦ለሰው ልጅ ከምንም በላይ ጤንነት እጅግ በጣም አስፈላጊና ወሳኝ ነገር ነው። ሰው በሕይወት ለመኖር ከየትኛውም ነገር በላይ ጤንነት ያስፈልጋል። ሰው ጤናማ ካልሆነ በሽተኛ ይሆናል። በሽተኛ ከሆነ ደግሞ ጊዜውን ያልጠበቀ እርጅና ይመጣል። ጊዜውን ያልጠበቀ እርጅና ተከትሎ ደግሞ ጊዜውን ያልጠበቀ ሞት ይመጣል። ለሁለቱም እርጅናዎች ላይ ጤንነት ጉልህ ምናን ይጫወታል። ✔#ጤንነት ስባል ከበሽታና ከህመም ስሜት ብቻ ነፃ መሆን አይደለም፡፡ ጤና የተሟላ #አካላዊ፣ #ስሜታዊ፣ #መንፈሳዊ እና #ማኀበራዊ ደህንነት ነው፡፡ መጀመሪያ ይሄ ግንዛቤ ውስጣችን ሊኖር ይገባል፡፡ አንድ ሰው አካላዊ፣ አእምሮአዊ፣ መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ጤንነቱ በሙሉ ተሟልቶ ሲገኝ ነው ሙሉ ጤነኛ ነው ልንል የምንችለው፡፡ እነዚህ ሁሉ ባልተሟሉበት ሁኔታ ውስጥ አንድ ሰው ህመም ስለማይሰማው ብቻ ጤነኛ ነው ሊባል ግን አይችልም፡፡ ሙሉ የሆነ የአካል፣ የስነልቦናዊ እንዲሁም የማኀበረሰባዊ ደኀንነት ነው::” ይለዋል፤ ይህም ሲባል የ...

አድሱን ሰው ልበሱ

Image
አዲሱን_ሰው_ልበሱ፡፡ •••••••••••••••••••• ✍የእግዚአብሔር ቃል በኤፌሶን 4፥24 “ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።” ይላል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ከመናገር በፍት በኤፌሶን 4፥22 “ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥” ይላል፡፡ አሮጌውን አስወግደን አዲሱን ለምን መልበስ እንዳለብን ደግሞ በቆላስይስ 3፥10 ላይ “የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል፤” እያሌ ምክንያቱን ያስቀምጣል፡፡ ✍ማነኛውም ዓይነት ክርስቲያን ዳግም የተወለደ፤ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድረገው የተቀበለ ሰው መልበስ ያለበት ምርጡ ልብስ አዲሱን ሰው ነው፡፡ ሰው ኢየሱስን እየተከተለ አሮጌውን ልብስ መልበስ በፍፁም አይሆንም፡፡ ሰው በአንድ ጊዜ የሰይጣንና የኢየሱስን በጋራ መልበስ አይችልም፡፡ ✍ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ክፍል  ✔"አሮጌ" ስለ ለማለት የፈለገው ፊተኛ፣ የቀድሞ፣ የድሮ፣ የጥንት፣ ያረጀ ማለት ነው፡፡ ✔ በለላ በኩለ ደግሞ "ፊተኛ ኑሮ"  ማለት የድሮ ባሕርይ፣ የቀድሞ ምልልስ ማለት ነው፡፡ ✍ሐዋርያው ጳውሎስ አሮጌውን ሰው አስወግዱ ሲል ✔በአሮጌው ሰው አካሄድ አትሂዱ ✔በአሮጌው ሰው አስተሳሰብ አትመሩ ወይም  ✔አሮጌው ሰው ዋጋ ለሚሰጠው ነገር ዋጋ አትስጡ ማለት ነው፡፡ ✍የሰው ልጅ አሮጌነትን የተላበሰው በቀዳማዊ አዳም በደል ምክንያት ነው፡፡ ቀዳማዊ አዳም አስቀድሞ በእግዚአብሔር መልክና አምሳል የተፈጠረ ቅዱስና እና ንፁሑ ባሕር ነበረው፡፡ መተዳደሪያውም ጽድቅና ቅድስና ብቻ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ይህን እስከ መጨረሻ መጠበቅ አልቻለም፡፡ ...

ለእኛ የተሰጠንን ሕይወት እንኑር

Image
#ለእኛ_የተሰጠንን_ሕይወት_እንኑር ▪▪▪▪▪▪▪▪▪▪▪▪ ⚫ለእኛ ከላይ ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ የተሰጠ፤ መኖር የሚገባኝ ውብና አስደናቂ  ሕይወት አለ። በጣም ብዙዎቻችን አሁን እየኖረን ያለነው የእኛ ሕይወት አይደለም። ብዙዎቻችን ለእኛ ከተሰጠው ሕይወት ውጭ ተራ ሕይወት እየኖረን ነው። ከዚህ የተነሳ የብዙዎቻችን ሕይወት ትርጉም አልባና ጣዕም የሌለው ሆኗል። ይህ ጉዳይ ደግሞ ማንነትን ከመርሳትና የሕይወት ዓላማን ከመሳት ጋር የተያያዘ ነው። ይህ አካሄድ እጅግ በጣም ከአደገኛ የሆነ ሰውን በምድር ላይ ተራና የማይረባ ሰው ከማድረግም አልፎ ከእግዚአብሔር መንግሥትም ጭምር ማስቀረት የሚችል መጥፎ አካሄድ ነው። ⚫ይህን ርዕስ በማስብበት ወቀት የአንድ መዶሻ ታርክ ትዝ አለኝ።  መዶሻው በመጀመሪያ የራሱን ሕይወት መኖር ያልቻለ በኃላ ግን የራሱን ማንነት ያገኘና ለእሱ የተሰጠውን ሕይወት መኖር የቻለ መዶሻ ነው። ታርኩን እነሆ፦ ◆ሰውየው መዶሻን ከገበያ ገዝተው ካመጣ በኃላ ለጊዜው ሳይጠቀምበት በዕቃ ማስቀመጫ ሳጥን ውስጥ ያስቀምጠዋል። መዶሻውም የራሱን ሕይወት ሳይኖር በሳጥን ውስጥ ተቀምጦ ይቆያል። በዚህ ጊዜ መዶሻው ምነው ሳጥን ውስጥ ታስሬ ተቀመጥኩ በማለት ማሰብ ይጀመራል። ምክንያቱም እሱ የተፈጠረው በሳጥን ውስጥ ለመቀመጥ አለመሆኑን ስለሚያውቅ። ዕለት በዕለት ያለምንም ሥራ በሳጥን ውስጥ ታሽጎ መቀመጡ ያሳስበዋል። በውስጡ ምንም ያህል የሚያሳስበው ጉዳይ ቢሆንም ለምን ታሸጎ እንደተቀመጠ ምክንያቱን ሊደርስበት አልቻለም። የሆነ  አንድ ችግር እንዳለ አውቆታል ነገር ግን ችግሩ ምን እንደሆን ማወቅ አልቻለም። ◆ከዕለታት አንድ ቀን ሰውየው መዶሻው ታሽጎ ከተቀመጠበት ሳጥን ውስጥ በማውጣት ለማገዶ የሚሆን ...

በአንዳች አትጨነቁ

Image
#በአንዳች_አትጨነቁ። (ፊልጵስዩስ 4፥6) ▪▪▪▪▪▪▪▪▪▪▪ ◆በመጽሐፍ ቅዱሳችን በተለይም በአድስ ኪዳን ውስጥ ኢየሱስ ደጋግሞ አትጨነቁ በማለት አማኞች በአንዳችም መጨነቅ እንደሌለባቸው በብዙ ቦታ ተናግሯል። ኢየሱስ በዮሐንስ 16፥33 ላይ “በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤” እንዳለ ሁሉ በዓለም ሳላችሁ የሚያስጨንቅ ነገር አለ። ይህ ባይኖር ኖሮ ኢየሱስ ደጋግሞ አትጨነቁ አይልም ነበረ። አትጨነቁ ያለው የሚያስጨንቅ ነገር ስላለ ነው። #ለመሆኑ_ጭንቀት_ምንድነው? ▪▪▪▪▪▪▪▪▪▪▪▪▪▪ ⚫ጭንቀት የሰውነትን ተፈጥሯዊ ሚዛን የሚያዛባ የአካል፣የአዕምሮና የስሜት ትንኮሳ የሚፈጥረው ምላሽ፣ ወይም የአንድ ሰው ፍላጎት ሊያንቀሳቅሰው ከሚችለው የግልና የማህበራዊ ሃብቶች አቅም በላይ ሆኖ ሲታየው የሚፈጠር ስሜት፣ ወይም ነገሮች ና ሁኔታዎች ከቁጥጥራችን እንደወጡ ስናስብ የሚፈጠር ስሜት ነው፡፡ ⚫ጭንቀት ማለት በስሜትም ሆነ አካለዊ በሆነ መንገድ ሰውነታችን ጠንካራ የአእምሮ ኬሚካሎችን እና ሆርሞኖችን ለማመንጨት የሚገደድበት ሁኔታ ነው፡፡ ይህ ጭንቀት ያለመረጋጋት፣ የመረበሽ ወይም የስጋት ስሜትን የሚያካትት ነው።  ⚫መጨነቅ ተፈጥሯዊ ነው። ሁላችንም የምንኖረው አስተማማኝ ባልሆነ ዓለም ውስጥ በመሆኑ አልፎ አልፎ ማናችንም በጭንቀት ስሜት ልንዋጥ እንችላለን። ጭንቀት በሁሉም ክልል ውስጥ ያሉ ሰዎችን የሚያጠቃ ነው። መጠኑና ጊዜው ይለያይ እንጂ ጭንቀት የማይነካው ሰው የለም፡፡ አንዳንድ ጊዜ እንዲህ የሚሉ ለምሳሌ ሰውየው ባለስልጣን ወይም ሀብታም ከሆነ “እንዴት እሳቸው ይጨነቃሉ?” በማለት ሰውየው ከማንኛውም ጭንቀት በየትኛውም ሁኔታና ጊዜ ነፃ ናቸው ብሎ የሚያምኑ ሰዎች አሉት። ሆኖም የትኛውም ሀብት ያለው፣ በየትኛውም እድሜ ክልል ያለውና በየትኛውም የስልጣን ...

ምርጥ ዕቃ መሆን

●"በትልቅም ቤት የእንጨትና የሸክላ ዕቃ ደግሞ አለ እንጂ የወርቅና የብር ዕቃ ብቻ አይደለም፥ እኵሌቶቹም ለክብር፥ እኵሌቶቹም ለውርደት ይሆናሉ፤ እንግዲህ ማንም ራሱን ከእነዚህ ቢያነጻ፥ ለክብር የሚሆን የተቀደሰም ለጌታውም የሚጠቅም ለበጎም ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ዕቃ ይሆናል። ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት ግን ሽሽ፥ በንጹሕም ልብ ጌታን ከሚጠሩ ጋር ጽድቅን እምነትን ፍቅርን ሰላምን አጥብቀህ ተከተል። ነገር ግን ጠብን እንዲያመጣ አውቀህ ከሰነፎችና ካልተማሩ ምርመራ ራቅ፤ የጌታም ባሪያ ለሰው ሁሉ ገር ለማስተማርም የሚበቃ ለትዕግሥትም የሚጸና ሊሆን እንጂ ሊጣላ አይገባውም።" 2ኛ ጢሞቴዎስ 2፡20-24 ♦ሐዋሪያው ጳውሎስ ይህን አስደናቂ መልዕክት የፃፈው እውነተኛ ልጁ ለሆነው በእምነት ለወለዳው ለተወደደው ለጢሞቴዎስ እንደሆነ በ2ኛ ጢሞቴዎስ 1፥2 ላይ እናያለን።  ♦ሐዋሪያው ጳውሎስ ይህን መልዕክት ለልጁ ለጢሞቴዎስ የፃፈው፦ 1) ጢሞቴዎስ ከሚጋፈጠው ስደት ባሻገር በእምነቱ እንዲበረታ ለማሳሰብ። በመጨረሻዎቹ ጥቂት ወራት ጳውሎስ ብቸኝነት ተጫጭኖት ነበር። ከጽሑፎቹ እንደምንመለከተው፥ ጳውሎስም እንደኛ ሰው በመሆኑ በአንዳንድ አማኞች ተግባራት ጥልቅ ስሜት ጉዳት ደርሶበት ነበር። ስደትን ከመፍራታቸው የተነሣ ይመስላል ብዙዎቹ የጳውሎስ የግል ጓደኞችና የአገልግሎት ተባባሪዎች ብቻውን ጥለውት ወደየቤቶቻቸው ገቡ። ጳውሎስ ከእስያ አውራጃ ሁሉም ሰው እንደ ተወው ይናገራል። ይህም በኤፌሶን አካባቢ የሚገኝ ስፍራ ሲሆን፥ ጳውሎስ ለረጅም ጊዜያት ያገለገለበት ቦታ ነበር (2ኛ ጢሞ.1፡15)። አብሮት ያገለግል የነበረው ዴማስ ትቶት ሄደ (2ኛ ጢሞ. 4፡10)። እነዚህ ሰዎች በክርስቶስ ማመናቸውን ይተዉ አይተዉ የታወቀ ነገር የለም። ነገር ግን ጳውሎስ እጅግ በሚፈልጋቸው...