አድሱን ሰው ልበሱ
አዲሱን_ሰው_ልበሱ፡፡ •••••••••••••••••••• ✍የእግዚአብሔር ቃል በኤፌሶን 4፥24 “ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።” ይላል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ከመናገር በፍት በኤፌሶን 4፥22 “ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥” ይላል፡፡ አሮጌውን አስወግደን አዲሱን ለምን መልበስ እንዳለብን ደግሞ በቆላስይስ 3፥10 ላይ “የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል፤” እያሌ ምክንያቱን ያስቀምጣል፡፡ ✍ማነኛውም ዓይነት ክርስቲያን ዳግም የተወለደ፤ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝ አድረገው የተቀበለ ሰው መልበስ ያለበት ምርጡ ልብስ አዲሱን ሰው ነው፡፡ ሰው ኢየሱስን እየተከተለ አሮጌውን ልብስ መልበስ በፍፁም አይሆንም፡፡ ሰው በአንድ ጊዜ የሰይጣንና የኢየሱስን በጋራ መልበስ አይችልም፡፡ ✍ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ክፍል ✔"አሮጌ" ስለ ለማለት የፈለገው ፊተኛ፣ የቀድሞ፣ የድሮ፣ የጥንት፣ ያረጀ ማለት ነው፡፡ ✔ በለላ በኩለ ደግሞ "ፊተኛ ኑሮ" ማለት የድሮ ባሕርይ፣ የቀድሞ ምልልስ ማለት ነው፡፡ ✍ሐዋርያው ጳውሎስ አሮጌውን ሰው አስወግዱ ሲል ✔በአሮጌው ሰው አካሄድ አትሂዱ ✔በአሮጌው ሰው አስተሳሰብ አትመሩ ወይም ✔አሮጌው ሰው ዋጋ ለሚሰጠው ነገር ዋጋ አትስጡ ማለት ነው፡፡ ✍የሰው ልጅ አሮጌነትን የተላበሰው በቀዳማዊ አዳም በደል ምክንያት ነው፡፡ ቀዳማዊ አዳም አስቀድሞ በእግዚአብሔር መልክና አምሳል የተፈጠረ ቅዱስና እና ንፁሑ ባሕር ነበረው፡፡ መተዳደሪያውም ጽድቅና ቅድስና ብቻ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ይህን እስከ መጨረሻ መጠበቅ አልቻለም፡፡ ...