የብርሃንና የጨው ማንነትን መግለጥ
13 እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም። 14 እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም። 15 መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል። 16 መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ። ማቴዎስ 5:13-16 ->ይህ ክፍል የተራራው ስብከት በመባል የሚታወቅና በማቴዎስ ወንገል ውስጥ ከሚገኙት አምስት ታላላቅ ትምርቶች አንዱና የመጀመርያ ነው። ->ኢየሱስ ይህን አገልግሎት ያካሄደው በገሊላ ከተማ ሆነው ነው ->ጌታ ኢየሱስ ይህ ትምህርት ስያስተምር ሁሉት ነገር በምሳሌ አንስቷል። ጨውና ብርሃን። 1. ጨውን ለምድር። 1.1. ምድር ስባል ደግሞ በምድር ላይ ያለው ፍጥረታት ሰውም ጭምር ስትሆን 1.2. በምድር ላይ ያሉ ሰዎች ነገር ግን በሕይወታቸው ጣዕም ያጡ ሕይወት መራራ የሆነባቸው ናት። 2. ብርሃንን ለዓለም። 2.1. ዓለም ስባል ደግሞ አሁን በእኛ ዘመኔ ያለች በክፋትና በተንኮል የተሞላች ዓለም ስትሆን 2.2. ያልዳኑ ጌታ ኢየሱስን ያልተቀበሉ በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ያሉ ሰዎች ወይም አሕዛብ ናት። @=>ጌታ ኢየሱስ ለሎችን ብዙ ዓይነት ምሳሌ መጠቀም እየቻለ ለምንድ ነው ጨውና ብርሃን መጠቀም የፈለገው? @ምክንያቱም ሰው ያለ ጨውና ያለ ብርሃን መኖር አይችልም። ሰው በሕይወት ለመኖር ከእግ/ር በታች ጨውና ብርሃን ያስፈልጋሉ። ->እንደዚህ ሁሉ እኛም ለዚህች ምድርና ዓለም እናስፈልጋለን ምክንያቱም “የፍጥረት ናፍቆት የእግዚአብሔርን ልጆች መገለጥ ...